Zelalem Eshete, Ph.D.
If we can’t accept each other as our own kind, based on the common denominator that we are all the same human beings, it is easier for us to be inhumane and do inhumane things to each other. We are all guilty and we take responsibility for our actions and inactions. Now, we all start to see each other as ones created in the image of God. There is no better honor for us to be identified than being known as God’s image bearer. I write this letter to those Oromo elites who have difficulty saying and meaning Ethiopia. I want to make a case for their need for a transformed heart to see and reflect the beauty of Ethiopia, which comprises more than 80 ethnics with nothing but grace and love in their beings. The fight among elites need to give way to the reality of the 100 million people who have a heart to see each other as beloved family. The Oromo elites are now on sacred ground to rise up to the destiny heaven has bestowed in the name – Oromo.
0 Comments
ዶ/ር ዘላለም እሸቴ
የሕዝብ መንግስት ለመመስረት ምርጫ ከማድረግ በፊት መንግስት የሚያስተዳድራት ሀገር ትወለድ። አሁን ያለን “ሀገር” ለቅርጫ ቀርባ ሁሉም ጎሣ ድንበሩን ለማስከበር ጦር እየመዘዘና ያልመዘዘው ለመምዘዝ አድፍጦ ጊዜ እየጠበቀ ነው።በቀረን ሁለት ዓመት ምርጫ ለማድረግ ከተነሳን፤ ሀገር እንድትወለድ መሰራት ያለበት ሥራ ለመስራት አንድ ቀን እንኳን ላይኖረን ነው። ባለ ሀገሩ ሀገር ሳይኖረው ንጉሶችን መምረጡ ምን ይፈይድለታል?ንጉሥ ለመሆን አራራ ያለው ካልሆነ በቀር፤ በሕዝብ ዘንድ ይህን ያህል ተቀባይነት ያለውን ጠቅላይ ሚኒስቴር ሀገርን እንዲያዋልዱ መተባበር ትልቅ ክብር ነው። ሀገሪቷ በጎሳ ተሸንሽና ሰላም ቢገኝ ኖሮ ሸንሽኖና ተለያይቶ መገላገል ይቻል ነበር። ግን ብዙ ንጉሶችን ፈጥሮ እርስ በርስ ያባላን እንደሆነ እንጂ መቼም ቢሆን የሰላም እንጀራ ልንበላ አንችልም። ምክንያቱም ተደበላልቀን ስናበቃ አሁን እንዴት ተሸንሽነን በድንበር ልንስማማ እንችላለን? የተደባለቅነው ወረቀት በእስፒል እንደተያያዘ ዓይነት ሳይሆን ወረቀት በሙጫ የተያያዘ ያህል ነው። በሙጫ የተጣበቁ ወረቀቶችን መለየት ፍዳ ነው። ከተሞከረ ደግሞ ሁሉም ይበጣጠሳል። ዶ/ር ዘላለም እሸቴ
አዲስ የኦሮምያ ካርታ ማውጣት የጊዜው መልስ ነውን? ፍቅር እንዲያሸንፍ ክርስቶስ ሰማይን ትቶ ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ። ያለዋጋ ፍቅር ሊያሸንፍ አይችልም። ስለዚህ ፍቅር በምድራችን እንዲያሸንፍ፤ ሁላችንም ከቡድንተኝነት አስተሳሰብ ወጥተን፤ ለጋራ ኢትዮጵያዊነት ልዕልና መኖር እንድንችል መያያዝ መቻል አለብን። ስንኖር ኢትዮጵያዊ፤ ስንሞት ኢትዮጵያ ነን የተባለው ትልቅ አባባል ነው። ስንኖር ኢትዮጵያዊ ነን ከማለታችን በፊት ግን ለግላዊ ቡድንተኝነት መሞት ያስፈልገናል። ኢትዮጵያዊነትን ለመኖር ከፈለግን፤ ከተከፋፈልንበት አጥር ወጥተን መያያዝ መቻል የግድ ይላል። ያለበለዚያ ኢትዮጵያዊነትን በፅንሰ ሀሳብ ደረጃ ብቻ የምናወራው ነገር እንጂ፤ የምንኖረው የሕይወት ዘይቤ ሊሆን አይችልም። |