myEthiopia.com
  • ደወል

የዘላለም እይታዎች 

አደራ ዶ/ር አብይ፥ ከዲያስፖራ

7/7/2018

0 Comments

 
ዶ/ር ዘላለም እሸቴ
 
የሚወድዎትና እርስዎም የሚወዱት ዲያስፖራ ጋር ለመገናኘት፤ በመካከል ያለውን ፈተና አምላክ እንድንወጣ ያስችለናል ብዬ አምናለሁ። በእግር ኳስ ጨዋታ ላይ ባለው በኢትዮጵያ ቀን ላይ ተገኝተው ሊያዩን ቢፈልጉም አምላክ ስላልፈቀደ አልተሳካም። ሁላችንም እንደ አንድ ሆነን እርስዎን ለመቀበል እየፈለግን ሳለ፤ ግን ስለ መምጣትዎ በሚደረገው ዝግጅት ላይ አለመግባባት ተፈጥሮ መሰናክል እንዳይኖር ጥንቃቄ እናደርግ ዘንድ ይገባል። የእርስዎ መንገድ የተዋጣለት እንዲሆን ሁላችንም ለክቡርነትዎ ዘብ እንቁም።
የተዋደደ ሳይገናኝ እንዲሁ አይቀርም።
 
አሜሪካ የሚመጡት የአሜሪካንን መንግስት ለማናገር ሳይሆን ሕዝብዎን ለማናገር ስለሆነ፤ ዲያስፖራን ወክለው የእርስዎ እንግዳ ተቀባይ አስተባባሪ እንዲሆኑ ኤምባሲው ይህንን ሃላፊነት ሙሉ ለሙሉ ለሕዝቡ ቢለቅ ጥሩ ነው። 
 
የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከአሜሪካ መንግስት ጋር በመተባበር የእርስዎን ደህንነት መጠበቅ ብቸኛ ስራቸው ቢሆን መልካም ነው።
 
“አንድ ዶላር በቀን” ያሉትን ወርቅ አስተሳሰብዎት የተቀደሰ ነውና፤ አደራ፥ ሲመጡ እባክዎን አካውንቱን ከፍተው ይምጡ። እኛን አናግረው ሲመለሱ ባዶ እጅዎን አይመለሱም። የወደፊቱ እርዳታችን በኩር የሚሆንና ሀገር የሚያኮራ ልግስና አድርገን፤ ፍቅራችንን ለሕዝባችን በስራ የምንገልፅበት ዕድል ይፈጥርልናል። ለዚህም መብቃታችን መታደል ነው።
 
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን አሰበ። ይጎበኛታልም።
0 Comments



Leave a Reply.

    Picture

    Archives

    December 2022
    August 2021
    July 2020
    November 2019
    October 2019
    September 2019
    August 2019
    July 2019
    June 2019
    April 2019
    February 2019
    December 2018
    October 2018
    August 2018
    July 2018
    June 2018
    May 2018
    April 2018
    October 2016

    Categories

    All

    RSS Feed

Copyright © 1999 - 2023
  • ደወል