myEthiopia.com
  • ደወል

በየትኛው ፍቅር እንደመር?

4/15/2019

0 Comments

 
በዋካንዳ ዘኢትዮጵያ 
 
ከዚህ በፊት “እንዴት በይቅርታ እንሻገር?” በሚል ርዕስ በጻፍኩት ጽሁፍ መጨረሻ ላይ “በፍቅር እንደመር” ላይ ለመጻፍ ቃል ገብቼ ስለነበርቃሌን ለማክበርና የፍቅርን ታላቅ ኃይል ለመጻፍ በማሰላሰል ላይ እያለሁ ተማሪ በነበርኩበት ጊዜ የተከሰተ አንድ ገጠመኝ ትዝ አለኝ:: 
 
“ዳይናሚክስ” የሚባል የ”ፊዚክስ” ዘርፍ ትምህርት አስተማሪየነበረ ኢጣሊያዊ፦  ለመፍታት ከባድ የሆነ ጥያቄ እንዴት እንደሚሠራ አሳየንና “ገብቷችኋል?” ብሎ ጠየቀን፤ ሁላችንም ዝም አልን:: “አልገባችሁም?” ብሎ እንደገና ጠየቀን፤ አሁንም ዝም አልን:: ከዚህ በኋላ የሚከተለውን በላቲን ቋንቋ ጥቁር ሰሌዳ ላይ በጠመኔ ጻፈ:: “Vox Clamantis in Deserto” ትርጉሙም “በምድረ በዳ የሚጮህ ሰው ድምፅ” ነው:: 
 
በአገራችን ኢትዮጵያ ወቅቱን በተመለከተ ብዙ መልካም ሐሳብ ያለባቸው ጽሁፎች፣ አውደ ጥናቶችና ንግግሮች ተደርገዋል፤ እየተደረጉም ነው:: በኢትዮጵያ ውስጥ የመጣውን ለውጥ አራማጆች:- ያለፉትን በደሎችና ስህተቶች ለታሪክ ተመራማሪዎች ትተን “በይቅርታ እንሻገር”፤ የተሰሩት በጎ ሥራዎች ላይ ለመጨመር “በፍቅር እንደመር”  የሚል መርሕ ይዘው ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ወደ የተሻለ አብሮ የመኖር፣ዴሞክራሲና እድገት ለማድረስ የሚያስችልን ጎዳና ለማስተካከልና የለውጡ በጎ አስተሳሰብ ተቋሟዊ እንዲሆን ሌትና ቀን እየሠሩ ይገኛሉ:: የእነዚህ መልካም አሳቢዎችና ለውጥ አራማጆች ድካም እንደ እኔ አስተማሪ ሰሚ ያጣ የምድረ በዳ ጩኸት ሆኖ ይሆን ወይ የሚል ስጋት አለኝ:: ምክንያቱም የብዙዎቻችን ጆሮዎች የሚከፈቱት ህዝብን ለሚያፋቅሩና ለችግሮቻችን ዘላቂ መፍትሔ ለሚያመጡ ሐሳቦች ሳይሆን ለተራ አሉባልታ፣ለጥላቻና ግልብ ጀብደኝነት በመሆኑ ነው::

Read More
0 Comments

    Amharic

    Archives

    January 2022
    October 2020
    August 2020
    April 2020
    November 2019
    September 2019
    July 2019
    April 2019
    November 2018
    October 2018
    September 2018
    August 2018
    July 2018

    Categories

    All
    Current Affairs
    Sport
    The God Factor Forum

    RSS Feed

Copyright © 1999 - 2023
  • ደወል