myEthiopia.com
  • ደወል

ደጉ ሳምራዊነት በህግ ተከልክሏል እንዴ?

8/12/2018

1 Comment

 
ላዕከ ታፈሰ 
​
እረ ለመሆኑ አገራችን ኢትዮጵያ ውስጥ “እንካ” ሞቶ ተቀበረ እንዴ? ፍቅርስ ማለት ባዶ የቃላት ጫጫታ ነው እንዴ?

በየቦታው ወገኖቻችን እየተገደሉና እየተፈናቀሉ ናቸው:: ምነው ሀብታሞች: የሐይማኖት ተቋማት: የፖለቲካ መሪዎች: የኢትዮጵያ ህዝብ ሁሉ እጃችሁ ታጠፈ: ልባችሁ ጨከነ?

የዶ/ር አቢይን የይቅርታና የፍቅር መልእክትን ወድጀዋለሁ: የእርሱን አመራር እደግፋለሁ ያለ ሁሉ ፍቅሩንና ይቅርታውን ማሳያ የሆኑት ወገኖቹ ሲቸገሩ ለምን ዝም አለ? ደጉ ሳምራዊነት በህግ ተከልክሏል እንዴ? ወይስ ሃላፊነቱ የክልልና የፌዴራል መንግስት ነው? ወይስ መንግስት መረዳዳትን ወንጀል ነው ብሎ ፈርጆታል?

ወደ ቤተክርስቲያንና መስጊድ በየቀኑ የሚሄደው የኢትዮጽያ ህዝብ ከዚያ ሲመለስ ሌላውን መግደልና ማፈናቀልን ከማን ተማረው? የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ ወይ ፈጣሪህ የሚልህን ታዘህ የሰውን ልጅ በእኩልነት መመልከትና በተግባር መውደድህን አሳይ:: እሱንም ካልቻልክ የይስሙላ እምነትህን ትተህ የአገራችንን ህግ አክብር:: 

ዶ/ር አቢይ “ፓወር ፖይንት” አዘጋጅና ለመላው ኢትዮጵያ ህዝብ መደመር: ይቅርታና ፍቅር ምን ማለት እንደሆነና ከእንግዲህ እያንዳንዱ ሰው ምን ማድረግ እንዳለበት: አንተም ከኛ ምን እንደምትጠብቅ እባክህ ንገረን:: ይህን በቶሎ አድርግልን:: ብዙ ሰው ይደግፍሃል እንጂ ፍልስፍናህን አልተረዳልህም ብዬ አምናለሁ::
1 Comment
Ted Seifu link
8/12/2018 10:22:44 pm

Good Point. And hope leaders in the faith community take this observation to actton soon.
Leadership is not a position really it is also an ACTION.
It is too soon to say but it seems Dr. Abye has a good vision and doctrine and lets pray this to penetrate to the people aa well.
Thanks
Ted

Reply



Leave a Reply.

    Amharic

    Archives

    January 2022
    October 2020
    August 2020
    April 2020
    November 2019
    September 2019
    July 2019
    April 2019
    November 2018
    October 2018
    September 2018
    August 2018
    July 2018

    Categories

    All
    Current Affairs
    Sport
    The God Factor Forum

    RSS Feed

Copyright © 1999 - 2023
  • ደወል